የፕሬስ መግለጫ

ግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም

አዲስ አበባ

የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 2,877,560 ኩንታል ምርትና አገልግሎት ለገበያ አቀረበ

ኮርፖሬሽኑ በ2015 በጀት ዓመት ያለፉት ዘጠኝ ወራት በሀገር ውስጥ እና በውጭ ገበያ ብር 9,046,004,247 ዋጋ ያለው 2,877,560 ኩንታል ምርትና አገልግሎት በማሰራጨት ዕቅዱን በመጠን 90 በመቶ በዋጋ ደግሞ 79 በመቶ አከናውኗል፡፡ የኮርፖሬሽኑ የሽያጭ መጠን ከ2014 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ40 በመቶ ብልጫ አለው፡፡ ከተገኘው ጠቅላላ ሽያጭ ገቢ 99.14 በመቶ ከሀገር ውስጥ ሽያጭ ገቢ የተገኘ ሲሆን ቀሪው 0.86 በመቶ ከኤክስፖርት የተገኘ ገቢ ነው፡፡

ኮርፖሬሽኑ ለሃገር ውስጥ ገበያ ብር 8,713,617,305 ዋጋ ያለው 2,832,037 ኩንታል ምርት እና አገልግሎት በማሰራጨት የዕቅዱን በመጠን 92 በመቶ በዋጋ ደግሞ 81 በመቶ አከናውኗል፡፡ የሀገር ውስጥ የፍጆታ ምርቶች በገቢ ድርሻ ሲታይ፡- እህልና ቡና 69.1%፣ የምግብ ዘይት 14.7%፣ ፍጆታ ዕቃዎች 6.7%፣ የኮንስትራክሽን ግብአቶች 5.27%፣ አትክልትና ፍራፍሬ 4.1 እና የግዥ አገልግሎት ሽያጭ 0.1 በመቶ ድርሻ ነበራቸው፡፡

የውጭ ሀገር ሽያጭን በተመለከተ በዘጠኝ ወራት 6,577 ኩንታል የተለያዩ የብርዕ፣ ጥራጥሬ፣ የቅባት እህሎች፣ ቡና እና ፍራፍሬ ሽያጭ በማድረግ 1,484,488 የአሜሪካን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡

ገበያን ለማረጋጋት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት

ኮርፖሬሽኑ አምራቹ ላመረተው ምርት ገበያ በመፍጠርና በተመጣጣኝ ዋጋ በመግዛት ለቀጣይ እንዲበረታታ ምርቱን በመረከብ እንዲሁም ሸማቹ ህብረተሰብ በአቅርቦት እጥረትና በገበያ ዋጋ መናር እንዳይጎዳ በቂ ምርት ካለበት እጥረት ወዳለበት በማጓጓዝ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያውን በማረጋጋት ጉልህ ሚና ይጫወታል፡፡

ለአምራቹ የገበያ እድል መፍጠር፡-

ኮርፖሬሽኑ 677,235 ኩንታል እህልና ቡና እንዲሁም 45,891 ኩንታል ፍራፍሬና አትክልት ከምርት አቅራቢዎች ግዥ አከናውኗል፡፡ በተጨማሪም የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎች ያመረቱትን ብር 1,894,485,726 ዋጋ ያለው 821,197 ኩንታል ምርት በመግዛት የገበያ ዕድል ፈጥሮላቸዋል፡፡

 

የአቅርቦት እጥረትንና የዋጋ ንረትን መከላከል፡- ኮርፖሬሽኑ የምርት አቅርቦት እጥረትንና የዋጋ ንረትን በመቀነስ ገበያውን ለማረጋጋት በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኩል ቅድሚያ ለሚሰጣቸው ተቋማት ማለትም ለሃገር መከላከያ ሰራዊት፣ ለአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን፣ ለፌደራል ፖሊስ፣ ለማረሚያ ቤትና ለሸገር ዳቦ ማምርቻ ፋብሪካ 1,669,686 ኩንታል የውጭ ሀገር ስንዴ ሽያጭ አከናውኗል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በሀገሪቱ የገጠመውን የምርት አቅርቦት እጥረት ለመሸፈን በተለይም ለዓለም ምግብ ድርጅት /WFP/ እና ለፋብሪካዎች ብር 696,634,233 ዋጋ ያለው 242,159 ኩንታል በቆሎ አሠራጭቷል፡፡ እንዲሁም ለመንግሥት ሠራተኞች፣ ለማረሚያ ቤቶችና ሌሎች ሸማች የህብረተሰብ ከፍሎች 57,408 ኩንታል ጤፍ፣ 42,426 ኩንታል ፍራፍሬና አትክልት፣ 11,402,300 ሊትር የምግብ ዘይት፣ 65,170 ኩንታል ስኳር እና 68,316 ኩንታል ልዩ ልዩ የፍጆታ ሸቀጦችን ለህብረተሰቡ አሰራጭቷል፡፡ በተጨማሪም በግንባታው ዘርፍ እየገጠመ ያለውን ከፍተኛ የሆነ የስሚንቶ አቅርቦት እጥረትና ዋጋ መናር ለመከላከል ከፋብሪካዎች በቀጥታ በመረከብ 459,328,067 ብር  ዋጋ ያለው 580,765 ኩንታል ሲሚንቶ ለተጠቃሚው በተመጣጣኝ ዋጋ ማስራጨት ተችሏል፡፡

15

የኮርፖሬሽኑ የምርት ስርጭት ዋጋ ከነፃ ገበያ ዋጋ ጋር ሲነፃፀር

ኮርፖሬሽኑ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለህብረተሰቡ ካቀረባቸው የመሠረታዊ ፍጆታ ምርቶች መካከል የተወሰኑትን አማካይ የመሸጫ ዋጋ ከነፃ ገበያ ዋጋ ጋር ሲነፃፀር የነበረው ልዩነት ከዚህ በታች ቀርቧል፡፡ ኮርፖሬሽኑ ለህብረተሰቡ የሸጠውን ብር 7.57 ቢሊዮን ዋጋ ያለው ምርት በወቅቱ በነበረው የገበያ ዋጋ ቢሽጥ ኑሮ ሊያወጣ ይችል የነበረ ዋጋ ብር 12.24 ቢሊዮን እንደሆነ ይገመታል፡፡ ኮርፖሬሽኑ የሸጠው አጠቃላይ ምርት ዋጋ ከገበያው ዋጋ በብር 4.67 ቢሊዮን የቀነሰ ነው፡፡ በዚህም ገበያውን ከማረጋጋት ባለፈ ህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶችን እንዲገበይ እገዛ አድርጓል፡፡

ነጭ ጤፍ፡- በነጻ ገበያ በኩንታል 7,100 ብር የተሸጠ ሲሆን ኮርፖሬሽኑ በብር 4,832.53 ለህብረተሰቡ አቅርቧል፡፡ ይህም 32 በመቶ የዋጋ ቅናሽ አለው፡፡

ስንዴ፡- በነጻ ገበያ በኩንታል 5,400 ብር የተሸጠ ሲሆን ኮርፖሬሽኑ በብር 2,978.85 ለህብረተሰቡ አቅርቧል፡፡ ይህም 45 በመቶ የዋጋ ቅናሽ አለው፡፡

ስኳር፡- በነጻ ገበያ በኪ.ግ 150 ብር የተሸጠ ሲሆን ኮርፖሬሽኑ በብር 75.00 (በኪ.ግ.) ለህብረተሰቡ አቅርቧል፡፡ ይህም 50 በመቶ የዋጋ ቅናሽ አለው፡፡

የፓልም ዘይት፡- በነጻ ገበያ በሊትር 135 ብር የተሸጠ ሲሆን ኮርፖሬሽኑ በብር 117.00 ለህብረተሰቡ አቅርቧል፡፡ ይህም 13 በመቶ የዋጋ ቅናሽ አለው፡፡

ፈሳሽ ዘይት፡- በነጻ ገበያ 200 ብር የተሸጠ ሲሆን ኮርፖሬሽኑ በብር 185.53 ለህብረተሰቡ አቅርቧል፡፡ ይህም 7 በመቶ የዋጋ ቅናሽ አለው፡፡

አቮካዶ፡- በነጻ ገበያ በኪ.ግ 60 ብር የተሸጠ ሲሆን ኮርፖሬሽኑ በብር 37 ለህብረተሰቡ አቅርቧል፡፡ ይህም 38 በመቶ የዋጋ ቅናሽ አለው፡፡

ብርቱካን፡- በነጻ ገበያ በኪ.ግ 150 ብር የተሸጠ ሲሆን ኮርፖሬሽኑ በብር 75 ለህብረተሰቡ አቅርቧል፡፡ ይህም 50 በመቶ የዋጋ ቅናሽ አለው፡፡

ሲሚንቶ፡- በነጻ ገበያ በኩንታል 1,500 ብር የተሸጠ ሲሆን ኮርፖሬሽኑ በብር 790.90 ለህብረተሰቡ አቅርቧል፡፡ ይህም 47 በመቶ የዋጋ ቅናሽ አለው፡፡